የተለያዩ የማህበረሰብ ክፍሎች በተሳፈተፉበት የንቅናቄ ማስጀመርያ ተቋማት ማስክ ላደረጉ ብቻ አገልግሎት በመስጠት ሰራተኞችም ሆኑ ተገልጋዮች የእጅ ንጽህናቸውን እንዲጠብቁ በማስገንዘብ ከንቅናቄው ጎን እንዲሰለፉ የጤና ሚንስትሯ ዶ/ር ሊያ ታደሰ አሳስበዋል፡፡፡፡
ትምህርት ቤቶች ውስጥ መምህራን እና አስተዳዳሪዎች፣ እያንዳንዱ ተማሪ ማስክ ማድረጉን ከመከታተልም ባለፈ፣ ተማሪዎች የእጅ ንጽህናቸውን እንዲጠብቁ፣ የህመም ምልክት ያለባቸው ካሉ፣ የባለሙያ እርዳታ እንዲያገኙ የሚችሉትን ሁሉ እንዲያደርጉም ጥሪ ቀርቧል፡፡
ማህበረሰቡ በአጠቃላይ ማስክን በተገቢው መንገድ እና በተገቢው ቦታ በማድረግ ሁሉም የንቅናቄው ተሳታፊ በመሆን ቫይረሱ ሊያስከትል የሚችለውን ከፍተኛ ቀውስ ለመግታት፣ የድርሻውን እንዲወጣ፣ ሚንስትሯ አሳስበዋል።
የ”እንድናገለግልዎ ማስክ ያድርጉ” ንቅናቄ ለመጪዎቹ ስድስት ወራት እንደሚቀጥል የጤና ሚኒስቴር አሳውቋል፡፡
Leave a Reply