የምርጫ ቦርዱ በተጨማሪ የአዲስ አበባ ከተማ እና የድሬደዋ ከተማ መስተዳድር የድምጽ መስጫ ቀን ሰኔ 5 መሆኑን ገልጿል።
ዝርዝር የጊዜ ሰሌዳውን ይፋ ያደረገው ቦርዱ የምርጫ ጊዜ ሰሌዳው የትግራይ ክልልን አያካትትም ብሏል፡፡
የምርጫ ቢሮዎች መከፈት የክልል መስተዳድር አባላት ከፍተኛ ትብብር ስለሚያስፈልገው፤ የክልሉ ጊዜያዊ አስተዳደር ይህንን ድጋፍ ለማድረግ ጊዜ ስለሚያስፈልገው እንዲሁም በክልሉ የታወጀው የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ለምርጫ በሚስማማ መልኩ መመቻቸቱ ሲረጋገጥ በክልሉ የሚደረገው ምርጫ ጊዜ ሰሌዳ ቦርዱ እንደሚያሳውቅም ምርጫ ቦርድ ዛሬ ባወጣው መግለጫ ጠቁሟል፡፡
Leave a Reply