ዋፋ ማርኬቲንግና ፕሮሞሽን፣ ፋና ብሮድ ካስቲንግ ኮርፖሬትና ዋልታ ቴሌቭዥን የሚሳተፉበት ትናንት የተጀመረው የክረምት የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ዛሬም ቀጥሏል፡፡ የዘመቻው አካል የሆኑ የበጎ ፈቃድ አገልግሎቶችም ዛሬ በጉጂ ዞን በአዶላ ከተማ ቀጥለዋል።
የሦስቱ ተቋማት ሠራተኞችና አመራሮች ዛሬ በአዶላ ከተማ የሚገኙ የአቅመ ደካማ ሰዎችን ቤቶች መልሶ የመገንባት መርሃ ግብር ያካሄዱ ሲሆን የችግኝ ተከላም ቀጥሎ የሚከናወን መርሃ ግብር ነው፡፡